8ኛው ከተማ አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራ ዐውደ ርእይ ተጠናቀቀ።

8ኛው ከተማ አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራ ዐውደ ርእይ ተጠናቀቀ።

“በሳይንስና ቴክኖሎጂ ፈጠራ የዳበረ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ1 ጀምሮ ለተከታታይ 3 ቀናት ሲካሄድ የነበረው ከተማ አቀፍ አውደርእይ ዛሬ በወዳጅነት አደባባይ የተለያዩ ደማቅ መርሃ ግብሮች ተሰንደውበት ተካሂዷል።

የመክፈቻ ንግግሩን ያደረጉት የአዲስ አበባ ት/ቢሮ ም/ሀላፊ በሳይንስና ቴክኖሎጂ አውደርእዪ ላይ 11 ክፍለ ከተሞች እና 2 አዳሪ ት/ቤቶችን የወከሉ ተወዳዳሪዎች እንደተሳተፉበት ገልፀዋል።

ውድድሩ በ1ኛ ደረጃ በሁለት ስርዓተ ትምህርቶች ማለትም በአማርኛ እና በአፋን ኦሮሞ፤ በሂሳብ ፣ በአካባቢ ሳይንስ እና በአጠቃላይ ሳይንስ የተካሄደ ሲሆን የውድድሩ ተሳታፊዎችም መምህራን እና ተማሪዎች ናቸው።

በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በሁሉም ክፍለ ከተሞች ተወዳድረው በአንደኝነት ውድድሩን አሸንፈው የተመረጡ ሲሆኑ በ5ቱ ዘፎች በሂሳብ ፣ በኬሚስትሪ ፣ በፊዚክስ ፣ በባዮሎጂ እንዲሁም በICT የትምህርት ዘርፎች ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ውድድሩ በልዩ ፋላጎት የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችንም እንዳካተተ ተመልክቷል።

በፋፃሜው ውድድር በአጠቃላይ ፈጠራ ውጤት ለሚኩራ ክ/ከተማ አሸናፊ ሲሆን በሽብርቅ ጭፈራ ደግሞ ጉለሌ ክ/ከተማ የመጀመሪያው አሸናፊ ሲሆን አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሁለተኝነቱን ይዞ ቦሌ ክ/ከተማ ደግሞ ሦሥተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል።

Leave a Reply